am_tw/bible/names/caesarea.md

1.1 KiB

ቄሳርያ፣ ፊልጶስ ቂሳርያ

ቂሳርያ ሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ፣ ከቀርሜሎስ ተራራ 39 ኪ.ሜ. ርቃ ትገኝ የነበረች በጣም ጠቃሚ ከተማ ነበረች። ፊልጶስ ቂሳርያ ከእስራኤል ሰሜን ምሥራቃዊ ክፍል አርሞንዔም ተራራ አጠገብ ያለች ከተማ ነበረች።

  • እነዚህ ከተሞች የሮም መንግሥትን ይገዙ ለነበሩ ቄሳሮች የተሰየሙት።
  • ኢየሱስ በተወለደበት ዘመን አካባቢ ባሕር ዳርቻ የነበረው ቂሳርያ የይሁዳ የሮም አውራጃ ከተማ ሆነች።
  • ሐዋርያው ጴጥሮስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአሕዛብ የሰበከው በቂሳርያ ነበር።
  • ጳውሎስ ከቂሳርያ በመርከብ ወደ ጤርሴስ ሄደ፤ በሁለተኛው ሐዋርያዊ ተልዕኮው በዚህች ከተማ ሁለት ጊዜ አልፏል።
  • ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በፊልጶስ ቂሳርያ ዙሪያ ወደ ነበሩ ከተሞች ተጉዘው ነበር።