am_tw/bible/names/bathsheba.md

855 B

ቤርሳቤህ

ቤርሳቤህ በዳዊት ሰራዊት ውስጥ ወታደር የነበርው የኦርዮን ሚስት ነበረች። ኦርዮን ከተገደለ በኋላ የዳዊት ሚስትና የሰሎሞን እናት ሆናለች

  • የኦርዮን ሚስት እያለች ዳዊት ከእርስዋ ጋር አመንዝሮ ነበር
  • ቤርሳቤህ ከዳዊት በፀነሰች ጊዜ ዳዊት ኦርዮን በጦርነት እንዲገደል አደረገ
  • ከዚያም ዳዊት ቤርሳቤህን አገባትና ልጃቸውን ወለደች
  • ከተወለደ ጥቂት ቀናት በኋላ ልጁ እንዲሞት በማድረግ እግዚአብሔር ዳዊትን በኃጢአቱ ቀጣው
  • እንደገና ቤርሳቤህ ሰሎሞን የተባለ ልጅ ወለደች፥ እርሱም አድጎ ከዳዊት በኋላ ንጉስ ሆነ