am_tw/bible/names/baruch.md

844 B

ባሮክ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ባሮክ በመባል የሚታወቁ የተለያዩ ሰዎች አሉ

  • አንደኛው ባሮክ የኢየሩሳሌምን ቅጥር በመጠገን ከነህምያ ጋር አብሮ ይሠራ የነበረው የዘባይ ልጅ ባሮክ ነው
  • ከዚህም በላይ በነህምያ ዘመን ቅጥሩ ከተሠራ በኋላ በኢየሩሳሌም መኖር ከጀመሩ መሪዎች አንዱ የነበረው የከልሐዜ ልጅ ባሮክ ነበር
  • ለየት ያለው የኔር ልጅ በሮክ የነብዩ ኤርምያስ ረዳት የነበረው ባሮክ ሲሆን፥ እግዚአብሔር ለነብዩ ኤርምያስ የሰጠውን መልዕክት በመጻፍና ያንን ለሕዝቡ ማንበብ በመሳሰሉ የተለያዩ ሥራዎች ኤርምያስን ረድቶታል