am_tw/bible/names/artaxerxes.md

1.2 KiB

አርጤክስስ

አርጤክስስ ከ 464-424 ዓቅክ የፋርስን መንግሥት ሲገዛ የነበረ ንጉሥ ነው

  • በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት ከይሁዳ የተወሰዱት እስራኤላውያን በዚያ ጊዜ በፋርስ ቁጥጥር ሥር በነበረችው በባቢሎን ምርኮ ውስጥ ነበሩ
  • ከባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው ለእስራኤላውያን የእግዚአብሔርን ሕግ እንዲያስተምሩ አርጤክስስ ለካህኑ ዕዝራና አብረውት ለነበሩ አይሁድ መሪዎች አርጤክስስ ፈቃድ ሰጠ
  • በዚሁ ጊዜ ጥቂት ቆየት ብሎ ከተማዋን የሚከብበውን ቅጥር የሚሠሩ አይሁድን እየመሩ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመለሱ አርጤክስስ ለወይን ጠጅ አሳላፊው ለነህምያ ፈቃድ ሰጥቷል
  • በዚያን ጊዜ ባቢሎን በፋርስ አገዛዝ ሥር ስለነበርች አንዳንዴ አርጤክስስ “የባቢሎን ንጉሥ” ተብሎ ይጠራል
  • አርጤክስስ አሐሻዊሮስ ከሚባለው ሰው ጋር አንድ እንዳይደለ ልብ በሉ