am_tw/bible/names/artaxerxes.md

10 lines
1.2 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-04 19:07:37 +00:00
# አርጤክስስ
አርጤክስስ ከ 464-424 ዓቅክ የፋርስን መንግሥት ሲገዛ የነበረ ንጉሥ ነው
* በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት ከይሁዳ የተወሰዱት እስራኤላውያን በዚያ ጊዜ በፋርስ ቁጥጥር ሥር በነበረችው በባቢሎን ምርኮ ውስጥ ነበሩ
* ከባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው ለእስራኤላውያን የእግዚአብሔርን ሕግ እንዲያስተምሩ አርጤክስስ ለካህኑ ዕዝራና አብረውት ለነበሩ አይሁድ መሪዎች አርጤክስስ ፈቃድ ሰጠ
* በዚሁ ጊዜ ጥቂት ቆየት ብሎ ከተማዋን የሚከብበውን ቅጥር የሚሠሩ አይሁድን እየመሩ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመለሱ አርጤክስስ ለወይን ጠጅ አሳላፊው ለነህምያ ፈቃድ ሰጥቷል
* በዚያን ጊዜ ባቢሎን በፋርስ አገዛዝ ሥር ስለነበርች አንዳንዴ አርጤክስስ “የባቢሎን ንጉሥ” ተብሎ ይጠራል
* አርጤክስስ አሐሻዊሮስ ከሚባለው ሰው ጋር አንድ እንዳይደለ ልብ በሉ