am_tw/bible/names/ararat.md

782 B

አራራት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “አራራት” ለአንድ አካባቢ፥ ለአንድ መንግሥትና የተራራ ሰንሰለት የተሰጠ ስም ነው።

  • “የአራራት ምድር” ምናልባት በአሁኑ ዘመን ቱርክ በሚባለው አገር ሰሜናዊ ምሥራቅ ክፍል የነበረ ቦታ ሊሆን ይችላል።
  • አራራት ይበልጥ የሚታወቀው የጥፋት ውሃ መቀነስ ከጀመረ በኋላ የኖህ መርከብ ያረፈችበት ተራራ ስም በመሆኑ ነው።
  • በዚህ ዘመን አንድ ተራራ፥ “የአራራት ተራራ” ተብሎ ከተጠራ ብዙውን ጊዜ የመጽሐፍ ቅዱሱ “አራራት ተራራ” ቦታ እንደሆነ ይታሰባል።