am_tw/bible/kt/power.md

1.1 KiB

ኀይል፣ ኀይላት

“ኀይል” የሚለው ቃል የሚያመለክተው አብዛኛውን ጊዜ በታላቅ ብርታት ነገሮችን ማድረግን ወይም ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ችሎታን ነው። “ኀይላት” የሚያመለክተው ነገሮች እንዲሆኑ የማድረግ ታላቅ ችሎታ ያላቸው ሰዎችን ወይም መናፍስትን ነው።

  • “የእግዚአብሔር ኀይል” ማንኛውንም ነገር በተለይም ለሰዎች የማይቻሉ ነገሮችን ለማድረግ እግዚአብሔር ያለውን ችሎታ ያመለክታል።
  • እግዚአብሔር በፈጠረው ማንኛውም ነገር ላይ ፍጹም ኀይል አለው።
  • እርሱ የሚፈልገውን እንዲያደርጉ እግዚአብሔር ለእሕዝቡ ኀይል ይሰጣል፤ ስለዚህ በሽተኞችን ሲፈውሱ ወይም ሌሎች ተአምራት ሲያደርጉ ያንን ያደረጉት በእግዚአብሔር ለይል ነው ማለት ነው።
  • ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስም እግዚአብሔር በመሆናቸው ይኸው ኀይል አላቸው።