2.1 KiB
2.1 KiB
ተአምር፣ ድንቅ፣ ምልክት
“ተአምር”እግዚአብሔር ራሱ ካላደረገው በቀር ጨርሶ ሊሆን የማይችል አስደናቂ ነገር ነው።
- ኢየሱስ ያደረጋቸው ተአምራት፣ ባሕርን ጸጥ ማሰኘትናን የዕውሩን ዐይን መክፈትንም ያካትታሉ።
- ሰዎችን በመደነቅና በመገረም ስለሚሙ “ተአምራት” አንዳንዴ፣ “ድንቆች” ተብለው ይጠራሉ።
- “ድንቅ” የሚለው ቃል አጠቃላይ በሆነ ሁኔታ የእግዚአብሔር ኀይልን መገለጥ ለምሳሌ፣ ሰማይና ምድርን በመፍጠር የተገለጠው ኀይሉን ያመለክታል።
- የእግዚአብሔርን ኀያልነትና አጽናፈ ዓለሙ ላይ ያለውን ፍጹም ሥልጣን የሚያሳዩ ወይም ማስረጃ የሚሆኑ ከመሆናቸው የተነሣ ተአምራት፣ “ምልክቶች” ተብለውም ይጠራሉ።
- የእስራኤልን ከግብፅ መውጣት፣ የዳንኤልን ከአንበሶች አፍ መዳን እንደ መሳሰሉት ነገሮች አንዳንድ ትአምራት የእግዚአብሔር ማዳን ሥራዎች ናቸው።
- በኖኅ ዘመን በምድር ሁሉ ላይ የጥፋት ውሃ ማምጣቱን፣ በሙሴ ዘመን በግብፅ ምድር መቅሠፍት ማምጣቱን የመሳሰሉ ሌሎች ድንቆች የእግዚአብሔር ፍርድ ሥራዎች ናቸው።
- አብዛኞቹ የእግዚአብሔር ተአምራት በሽተኞችን መፈሰስ ወይም የሞቱ ሰዎችን ማስነሣት ናቸው።
- ሰዎችን ሲፈውስ፣ ባሕርን ጸጥ ሲያደርግ፣ በባሕር ሲራመድ፣ የሞቱ ሰዎችን ሲያስነሣ የእግዚአብሔር ኀይል በኢየሱስ አማካይነት ተገልጧ። አንዚህ ሁሉ ተአምራት ናቸው።
- የፈውስ ተአምራትንና በእግዚአብሔር ኀይል ብቻ የሚቻሉ ነገሮችን እንዲያደርጉ ለነቢያትና ለሐዋርያት ተአምራት የማድረግ ችሎታን ሰጥቷቸው ነበር።