11 lines
1.5 KiB
Markdown
11 lines
1.5 KiB
Markdown
|
# ፈተና
|
||
|
|
||
|
“ፈተና” የሚለው ቃል የአንድን ሰው ብርታትና ድካም ለይቶ የሚያሳይ አስቸጋሪ ወይም አዳጋች ሁኔታ ያመለክታል።
|
||
|
|
||
|
* የሰዎችን ኀጢአት ለመግለጥ አንዳንዴ እግዚአብሔር በሚመጡ ፈተናዎች ይጠቀማል። ፈተና ሰዎች ከኀጢአት እንዲመለሱና ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርቡ ይረዳል።
|
||
|
* ምን ያህል ንጹሕ ወይም ጠንካራ መሆናቸውን ለመለየት ወርቅና ሌሎች የብረት ዐይነቶች በእሳት ይፈተናሉ። ይህ እግዚአብሔር ሕዝቡን ለመፈተን አዳጋችና አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እንደሚጠቀም የሚያመለክት ሥዕል ነው።
|
||
|
* እግዚአብሔር ሰዎችን ይፈትናል፤ ይሁን እንጂ ኀጢአት እንዲያደርጉ ምክንያት የሚሆን ፈተና አያመጣባቸውም፤ ሰይጣን ሰዎችን የሚፈትነው ኀጢአት እንዲፈጽሙ ለማድረግ ነ።ው
|
||
|
* “መፈተን” የአንድ ሰው ወይም ነገር ትክክለኛ ምንነት ይፋ እንዲወጣ መገዳደር” ማለት ነው።
|
||
|
* እግዚአብሔርን መፈተን ባለ መታዘዝ መጽናት፣ ለምሕረቱ ዋጋ አለመስጠት ማለት ነው።
|
||
|
* እግዚአብሔርን መፈተን እንደማይገባ ኢየሱስ ለሰይጣን ነግሮታል። እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ፣ ቅዱስና ከማንኛውም ነገር በላይ ነው።
|