20 lines
1.3 KiB
Markdown
20 lines
1.3 KiB
Markdown
# አጠቃላይ መረጃ
|
|
|
|
ያህዌ ለእስራኤል ሕዝብ መናገር ቀጥሏል፡፡
|
|
|
|
# ስለ ስሜ ስል ቁጣዬን አዘገያለሁ
|
|
|
|
እዚህ ላይ፣ ‹‹ስም›› የያህዌን ማንነት ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ስለ ማንነቴ ስል ቁጣዬን አዘገያለሁ››
|
|
|
|
# ስለ ክብሬ ስል እናንተን ከማጥፋት እታቀባለሁ
|
|
|
|
ይህ የዐረፍተ ነገሩ ክፍል ከመጀመሪያው ክፍል ጋር በመሠረቱ ተመሳሳይ ነው፡፡
|
|
|
|
# እነሆ፣ እንደ ብር ባይሆንም፣ አንጥሬሃለሁ፤ በመከራ እቶን አንጽቼሃለሁ
|
|
|
|
እነርሱ የከበሩ ማዕድኖች የሆኑ ይመስል እቶን ደግሞ እነርሱን የሚያነጻ እሳት ይመስል ያህዌ ሕዝቡን በመከራ ውስጥ እንደሚያነጻ ይናገራል፡፡
|
|
|
|
# ስሜን ለውርደት እንዴት አሳልፌ እሰጣለሁ?
|
|
|
|
ያህዌ ጥያቄውን ያቀረበው ስሙን ለውርደት አሳልፎ እንደማይሰጥ አጠንክሮ ለማመልከት ነው፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ማንም ስሜን እንዲያዋርድ አልፈቅድም››
|