am_tn/deu/26/06.md

1.1 KiB

ከፉብን፣ አሰቃዩንም

በመሠረቱ እነዚህ ሁለት ሐረጎች የሚሉት አንድ ነገር ነው። ግብፃውያን የጭካኔ ተግባር እንደ ፈጸሙባቸው አጽንዖት ይሰጣሉ። (See: Doublet)

አደረገብን

እዚህ ጋ “እኛ” የሚያመለክተው በግብፅ ይኖሩ የነበሩትን የእስራኤል ሕዝብ ነው። ተናጋሪው በግብፅ ቢኖርም ባይኖርም ራሱን ከሕዝቡ አንዱ አድርጎ ይጨምራል። (See: Inclusive “We”)

ድምፃችንን ሰማ

እዚህ ጋ “ድምፅ” የሚያመለክተው ሙሉውን ሰው እና ጩኸቱን ወይም ጸሎቱን ነው። አ.ት፡ “ጩኸታችንን ሰማ” ወይም “ጸሎታችንን ሰማ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ስቃያችንን፣ ልፋታችንን እና መጨቆናችንን

“ግብፃውያን ያሰቃዩን የነበረውን፣ ስንሠራው የነበረውን በጣም ከባድ የሆነውን ሥራ እና ግብፃውያኑ ይጨቁኑን የነበረውን”