24 lines
1.3 KiB
Markdown
24 lines
1.3 KiB
Markdown
|
# ያህዌን ፈለግሁት
|
||
|
|
||
|
‹‹ፈለግሁት›› የሚለው ዳዊት ያህዌ እንዲረዳው መለመኑን ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወደ ያህዌ ጸለይሁ›› ወይም፣ ‹‹እንዲረዳኝ ያህዌን ለመንሁ››
|
||
|
|
||
|
# ወደ እርሱ የሚመለከቱ
|
||
|
|
||
|
‹‹መመልከት›› ከእርሱ ርዳታ መለመንን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹እንዲረዳቸው ወደ እርሱ የሚመለከቱ›› ወይም፣ ‹‹ከእርሱ ብቻ ርዳታ የሚጠብቁ››
|
||
|
|
||
|
# ያበራሉ
|
||
|
|
||
|
ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር ደስ ይላቸዋል ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ደስ ይላቸዋል››
|
||
|
|
||
|
# ፊታቸውም አያፍርም
|
||
|
|
||
|
‹‹ፊታቸው›› ወደ ያህዌ የሚመለከቱ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አያፍሩም›› ወይም፣ ‹‹ይኮራሉ››
|
||
|
|
||
|
# ይህ ችግረኛ
|
||
|
|
||
|
ዳዊት ራሱን እንደ ችግረኛ ይቆጥራል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ተቸግሬ ነበር››
|
||
|
|
||
|
# ያህዌ ሰማው
|
||
|
|
||
|
‹‹ሰማኝ›› ያህዌ ረዳኝ ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ያህዌ ረዳው››
|