am_tw/bible/kt/heart.md

991 B

ልብ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልብ የሰውን ሐሳብ፣ ስሜት፣ ፍላጎት ወም ፈቃድ ለማመልከት ብዙውን ጊዜ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

  • “ልበ ጠንካራ” መሆን ሰውየው በግትርነት ለእግዚአብሔር መታዘዝ አለመፈለጉን የሚያሳይ የተለመደ አገላለጽ ነው።
  • “በፍጹም ልቤ” ወይም፣ “በሙሉ ልቤ” የተሰኙት አገላለጾች ምንም ወደ ኋላ ሳይባል፣ በሙሉ መሰጠትና ፈቃደኛነት አንድን ነገር ማድረግን ያመለክታሉ።
  • “በልብህ ያዘው” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ለአንድ ሰው የተለየ ከበሬታ መስጠት ማለት ነው።
  • “ልበ ሰባራ” የሚለው ሐረግ ከፍ ያለ ሐዘንን ያመለክታል። የሰውየው ስሜት በከፍተኛ ደረጃ ተጎድቷል ማለት ነው።