am_tw/bible/kt/favor.md

1.2 KiB

ሞገስ፣ ሞገስ ያለው፣ አድልዎ (ከሌሎች የተለየ ሞገስ የሚደረግለት)

ሞገስ እርሱን በተመለከተ ጥሩ አመለካከት ያለንን ሰው ለመጥቀም የሚደረግ ነገርን ያመለክታለ። “ሞገስ ያለው” ነገር ቀና ተቀባይነት ያለው ወይም ጠቃሚ ነው።

  • “አድልዎ” ለአንዱ ሞገስ ማሳየት ለሌላው ግን ሞገስ መንፈግ ነው። አንዳንዴ ሰዎች ሀብታም ወይ ታዋቂ በመሆናቸው ብቻ ከሌላው የተለየ ሞገስ (አድልዎ) ይደረግላቸዋል።
  • ኢየሱስ፣ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት፣ “ሞገስ በማግኘት አደገ።” ይህም ፀባይና ባሕርዩ በእነርሱ ዘንድ ተቀባይነት ነበረው ማለት ነው።
  • “ሞገስ አገኘ” የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር በሌሎች ዘንድ መወደድን ተቀባይነት ማግኘትን ያመልክታል።
  • አንድ ንጉሥ ለሰው ሞገስ አደረገ ማለት ያ ሰው ያቀረበው ልመና በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አገኘ ማለት ነው።