am_tw/bible/kt/adultery.md

9 lines
1.1 KiB
Markdown

# ዝሙት፣ዘማዊነት፣ዘማዊ፣ዘማዊት
“ዝሙት” አንድ ያገባ ሰው የትዳር ጓደኛው ካልሆነች ጋር ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸምን ኃጢአት ያመለክታል። “ዘማዊነት”የዚህ ዐይነት ተግባርን ወይም ይህን ኃጢያት የሚያደርግ ሰው ድትጊት ያመለክታል።
* አንዳንዴ “ዘማዊት” የሚለው ቃል ዝሙት የፈጸመችው ሴት መሆንዋን ለይቶ ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።
* ዝሙት ባልና ሚስት በጋብቻ ኪዳን አንዳቸው ለሌላው ያገቡትን ቃል ያፈርሳል።
* ዝሙት እንዳያደርጉ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዝዟል።
* ብዙውን ግዜ ዘማዊነት የሚለው ቃል የእስራኤል ሕዝብ ለእግዚአብሔር ታማኝ ያልሆኑበትን በተለይ ደግሞ ሐሰተኛ አማልክትን ያመለከበትን ሁኔታ ለመግለጽ ምሳሌያዊ በሆነ ቋንቋ ጥቅም ላይ ውሏል።