am_tw/bible/other/witness.md

1.1 KiB

ምስክር፣ የዓይን ምስክር

“ምስክር” የሆነውን ነገር በግል የሚያውቅ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ምስክር የሚባለው እውነት መሆኑን የሚያውቀውን የሚናገር ሰው ነው። “የዓይን ምስክር” እዚያ የነበረና የሆነውን ሁሉ በዓይኑ የተመለክተ ሰው ነው።

  • አንድን ነገር፣ “መመስከር” የሆነውን ነገር ማየት ማለት ነው።
  • ምስክር፣ ፍርድ ቤት ቀርቦ ሲሆን ያየውን ወይም የሰማውን ይመሰክራል።
  • ምስክሮች ስላዩትና ስለሰሙት እውነቱን መናገር ይጠበቅባቸዋል
  • እውነቱን የማይናገር ምስክር፣ “የሐሰት ምስርክ” ይባላል።
  • “በመካከላችን ይመስክር” ማለት በመካከላችን ስለ ተደረገው ውል ማስረጃ ይሁን ማለት ነው። ምስክሮች እያንዳንዱ ሰው የሚገባውን እያደረገ መሆኑን ያረጋግጣሉ።