am_tw/bible/other/winepress.md

673 B

ወይን መርገጫ

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ወይን መርገጫ የወይን ጠጅ ለመሥራት የወይኑ ፍሬ የሚረገጥበት ቦታ ነው።

  • የእስራኤል ወይን መርገጫ መሬት ላይ የተቆፈረ ትልቅ፣ ሰፊ ጉድጓድ ነበር። የወይኑ ዘለላዎች ታችኛው የጉድጓዱ ጠፍጣፋ ቦታ ላይ ይደረጉና የወይኑ ጭማቂ እንዲወጣ ሰዎች በእግራቸው ይረግጡት ነበር።
  • ወይን መርገጫ የእግዚአብሔር ቁጣ ሕዝቡ ላይ መፍሰሱን ለማሳየት በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።