am_tw/bible/other/wheat.md

694 B

ስንዴ

ስንዴ ሰዎች ለምግብ የሚያመርቱት እህል ነው።

  • ዘሩ የሚገኘው የስንዴው ተክል ጫፍ ላይ ነው።
  • ስንዴት ከታጨደ በኋላ ፍሬው ከገለባው ይለያል። ይህ ሂደት፣ “መውቃት” ይባላል።
  • ብዙውን ጊዜ የስንዴው ገለባ ወይም አገዳ ከብቶች እንዲተኙበት መሬት ላይ ይደረጋል።
  • ከስንዴው ጋር የሚበቅል ትንሽ ዘር እንክርዳድ ይባላል፤ ለምንም የሚጠቅም ስላልሆነ ይጣላል።
  • ሰዎች ስንዴውን ፈጭተው ዱቄቱን ዳቦ ለመሥሪያ ይጠቀሙበታል።