am_tw/bible/other/watchtower.md

1004 B

መጠበቂያ ግንብ

“መጠበቂያ ግንብ” ጠባቂዎች እዚያ ላይ ሆነው ማንኛውንም አደጋ የሚመለከቱበት ቦታ እንዲሆን የተሠራ ረጅም ግንብ ነው። እነዚህ ግንቦች አብዛኛውን ጊዜ የሚሠሩት ከድንጋይ ነው።

  • እነርሱ ላይ ሆነው እህላቸውን ሌቦች ከመሰረቅና ከእንስሳት ለመጠበቅ ባለ ርስቶችም መጠበዚያ ግንብ ይሠራሉ።
  • ብዙውን ጊዜ ግንቡ ጠባቂዎቹ ከነቤተሰባቸው የሚኖርበት ክፍሎችም ይኖሯቸዋል፤ በዚህ ሁኔታ ለሊትና ቀን በጥበቅ ይተጋሉ።
  • ጠላት ከተማዋን ለማጥቃት ሲመጣ ማየት እንዲቻል የከተማ መጠበቂያ ግንቦች ከከተማዋ በጣም ከፍ እንዲል ተደርጎ ይሠራል።
  • መጠበቂያ ግንብ ከጠላቶች የመጠበቅና ከለላ የማግኘት ምሳሌ ነው።