am_tw/bible/other/tradition.md

1.2 KiB

ባሕል

ባሕል የሚያመለክተው ለረጅም ዘመን የተያዘና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ ወግ ወይም ልማድ ነው።

  • እስራኤላውያን ይዘዋቸው የነበሩ ብዙ ባሕሎች በጊዜ ሂደት በኋላ የሃይማኖት መሪዎቹ የጨምሩት እንጂ በብሉይ ኪዳን የታዘዙ አልነበሩም።
  • አንዳንድ ጥቅሶች “የሰዎችን ባሕሎች” ይዘዋል፤ ይህም አይሁድ ይለማመዷቸው የነበሩ በኋላ የተጨመሩ እንጂ፣ የእግዚአብሔር ትእዛዞች እንዳልሆኑ ግልጽ ያደርጋል።
  • አንዳንድ፣ “ባሕሎች”እግዚአብሔር የሰጠው ትእዛዞችንና እንዲሁም የሰዎች ሃይማኖታዊ ባሕልን ያካተቱ በመሆናቸው አጠቃላይ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ ይውላሉ።
  • በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያኖች የሚለማመዷቸው ብዙ ባሕሎች የቅዱሳት መጻሕፍት ድጋፍ የላቸውም፤ ይሁን እንጂ፣ በታሪክ ውስጥ ተቀባይነት እያገኙ የመጡ ልማድና አሠራሮች ናቸው።