am_tw/bible/other/suffer.md

814 B

መከራ፣ መከራ መቀበል

“መከራ” እና፣ “መከራ መቀበል” የተሰኙት ቃሎች በሽታን፣ ስቃይን ወይም ሌሎች አዳጋች ነገሮችን የመሳሰሉ አስከፊ ነገሮች ማለት ነው

  • ሰዎች ሲሰደዱ ወይም ሲታመሙ መከራ ይደርስባቸዋል
  • አንዳንዴ ሰዎች ላይ መከራ የሚደርሰው ራሳቸው በፈጸሙት መጥፎ ነገር ሊሆን ይችላል፤ አንዳንዴ ግን በዓለም ካለው ኅጢአትና ስቃይ የተነሣ ሊሆን ይችላል
  • መከራ ስቃይን ወይም ሕመምን የመሰለ አካላዊ ጉዳት ሊሆን ይችላል። ፍርሃትን፣ ሐዘንና በቸኝነትን የመሰለ መንፈሳዊ ጉዳት ሊሆንም ይችላል