am_tw/bible/other/storehouse.md

1.3 KiB

ጎተራ

“ጎተራ” ምግብ ወይም ሌሎች ነገሮችን ለማከማቸት የሚያገለግል ማስቀመጫ ነው

  • መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈበት አመን አብዛኛውን ጊዜ፣ “ጎተራ” ጥቅም ላይ የሚውለው ከረሃብ የተነሣ የምግብ እጥረት ሲኖር ለመጠቀም ትርፍ እህልንና ሌሎች ምግቦችን ለማከማቸት ነበር
  • አንዳንድ ጊዜ የቤተሰቡን ሀብት ለማጠራቅም ጎተራ ጥቅም ላይ ይውላል
  • ይህ ቃል ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ፣ እግዚአብሔር ለሕዝቡ መስጠት የሚፈልገውን መልካም ነገር ሁሉ ያመልክታል
  • ከተሸነፉ ጠላቶች የተወሰዱና ለያህዌ የተቀደሱ ዋጋ ያላቸው ነገሮች ሁሉ የሚጠበቁት ያህዌ ቤት ውስጥ ባለው ጎተራ ነበር። ይህ ሀብት ቤተመቅደስን ማደሻ እንዲሆን ይከማቻል። አንዳንዴም፣ “ግምጃ ቤት” ይባላል
  • “ጎተራ” የሚለውን ቃል ለመተርጎም ጥቅም ላይ መዋል የሚችሉ ቃሎች፣ “እህል ማጠራቀሚያ” ወይም፣ “ምግብ ማከማቻ” ወይም፣ “ዋጋ ያላቸው ነገሮች የሚቀመጡበት” የተሰኙት ናቸው