am_tw/bible/other/send.md

1.5 KiB

ላከ፣ መላክ

“ላከ” አንድ ሰው ወይም አንድ ነገር ወደ ሌላ ቦታ እንዲሄድ ማድረግ ማለት ነው። አንድን ሰው፣ “መላክ” አንድን ነገር እንዲያደርግ ወይም አንድን ተልዕኮ እንዲፈጽም መናገር ወይም ማዘዝ ማለት ነው

  • ሰዎች የሚላኩበት ራሱን የቻለ ዓላማ ይኖራል። ብዙ ጊዜ የሚላከው ሰው የተላከበትን ጉዳይ የመፈጸምና የማስፈጸም ኅላፊነትም ይሰጠዋል
  • “ዝናብ ላከ” ወይም፣ “መዐት ላከ” የተሰኙት ሐረጎች፣ “እንዲመጡ ማድረግ” የሚል ትርጉም አላቸው። ይህ ዐይነቱ አነጋገር ጥቅም ላይ የሚውለው እግዚአብሔር እነዚህ ነገሮች እንዲሆኑ በሚያደርግበት ጊዜ ነው
  • “ቃል ላከ” ወይም፣ “መልእክት ላከ” በተሰኙት አነጋገሮች ውስጥ፣ “ላከ” ጥቅም ላይ በሚውልበት ጊዜ፣ ለሌሎች የምንናገረው ቃል ወይም መልእክት ሰጠን የሚል ትርጉም ይኖረዋል
  • ለአንድ ሰው አንድ ዓይነት እንስሳ ወይም አንድ ነገር መላክ፣ እነዚያን ነገሮች ለሰውየው መስጠት ማለት ነው፤ ብዙውን ጊዜ እነዚህን ነገሮች ለተቀባዩ ለማድረስ ጥቂት ጉዞ ማድረግ ያስፈልግ ይሆናል