am_tw/bible/other/reign.md

773 B

መግዛት

መግዛት በአንድ አገር ወይም በአንድ መንግሥትና ሕዝቡ ላይ ንጉሥ መሆን ማለት ነው። አንድ ንጉሥ የሚገዛው እርሱ በሕይወት እስካለ ድረስ ነበር።

  • የአጽናፈ ዓለሙ ፈጣሪ ሁሉን የሚችል እግዚአብሔር መላውን ዓለም በንጉሥነቱ ይገዛል።
  • እርሱ ንጉሣቸው እንዳይሆን ሲፈልጉ እስራኤል የራሳቸው ንጉሦችን እንዲያነግሡ እግዚአብሔር ፈቀደ።
  • ኢየሱስ ክርስቶስ ሲመለስ መላውን ዓለም በንጉሥነት እንደሚገዛና ክርስቲያኖችም ከእርሱ ጋር እንደሚነግሡ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።