am_tw/bible/other/rebuke.md

790 B

መገሠጽ

መገሠጽ በቃል ጠበቅ ያለ እርማት መስጠት ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እንዲህ የሚደረገው ያንን ሰው ከኀጢአት ለመመለስ ነው።

  • ክርስቲያኖች ለእግዚአብሔር የማይታዘዙ ሌሎች አማኞችን መገሠጽ እንዳለባቸው አዲስ ኪዳን ያዝዛል።
  • ልጆቻቸው አልታዘዝም ካሉ ሊገሥጿቸው እንደሚገባ መጽሐፈ ምሳሌ ወላጆችን ያሳስባል።
  • ጠንከር ያለ ተግሣጽ የሚሰጠው በደል የፈጸመ ሰው ከዚያ የበለጠ ኃጢአት እንዳያደርግ ነው።
  • ይህ ቃል፣ “ጠንከር ያለ እርምት” ወይም፣ “ምክር” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።