am_tw/bible/other/raise.md

13 lines
1.5 KiB
Markdown
Raw Permalink Blame History

This file contains ambiguous Unicode characters

This file contains Unicode characters that might be confused with other characters. If you think that this is intentional, you can safely ignore this warning. Use the Escape button to reveal them.

# መነሣት፣ ተነሣ
በአጠቃላይ፣ “መነሣት” “ብድግ ማለት” ወይም፣ “ወደ ላይ መውጣት” ማለት ነው።
* ምሳሌያዊ በሆነ አነጋገር፣ “ተነሥ” ማለት አንድ ነገር ወደ መገኘት እንዲመጣ ወይም እንዲታይ ማድረግ ማለት ነው። አንዳች ነገር እንዲያደርግ ሰውን መሾም ማለትም ይሆናል።
* አንዳንዴ፣ “ተነሥ” ማለት፣ “መመለስ” ወይም “እንደ ገና መሠራት” ማለትም ይሆናል።
* “ከሞት ተነሣ” የሚለው ሐረግ ውስጥ ያለው፣ “ተነሣ” ልዩ ትርጕም አለው፤ የሞተው ሰው እንደ ገና ወደ ሕይወት ሲመጣ ማለት ነው፥
* አንዳንዴ፣ “መነሣት” - አንድን ሰው ወይም ነገር ወደ ላይ ከፍ ማድረግን ያመለክታል።
* መነሣት፣ ተነሣ፣ “ወደ ላይ መሄድ” ማለትም ይሆናል።
* አንድ ሰው ወደ አንድ ቦታ ለመሄድ ከተነሣ፣ “ተንሥቶ ሄደ” ወይም፣ “ብድግ ብሎ ሄደ” ማለት ነው።
* አንድ ነገር፣ “ተነሣ” ከተባለ፣ “ሆነ” ወይም፣ “መሆን ጀመረ” ማለት ነው።
* ኢየሱስ ከሞት እንደሚነሣ አስቀድሞ ተናግሮ ነበር፤ ኢየሱስ ከሞተ ሦስት ቀን በኋላ መልአኩ፣ “ተነሥቶአል!” አለ።