am_tw/bible/other/proclaim.md

1.1 KiB

ማወጅ፣ ዐዋጅ

አንድን ነገር በሕዝብ ፊት እና በድፍረት መናገር ወይም ማሳወቅ ማወጅ ይባላል።

  • ብዙውን ጊዜ መጸሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ማወጅ” የሚለው እግዚአብሔር ያዘዘውን በግልጽ መናገርና እርሱ ምንኛ ታላቅ መሆኑን ለሌሎች መናገር ነው።
  • ከአዲስ ኪዳን እንደምንመለከተው ሐዋርያት በተለያዩ ከተሞችና አካባቢዎች ላሉ ብዙ ሰዎች የኢየሱስን የምሥራች ቃል ተናግረዋል።
  • “ማወጅ” የሚለው ቃል ነገሥታት የሚያወጧቸውን ደንቦች ወይም ክፉ ነገርን በአደባባይ ማውገዝ ያመለክታል።
  • “ማወጅ” የሚለውን ለመተርጎም፣ “ማሳወቅ” ወይም፣ “በግልጽ መስበክ” ወይ፣ “በአደባባይ መናገር” በተሰኙ ቃሎች መጠቀም ይቻላል።
  • “ዐዋጅ” የሚለው ቃል፣ “ማስታወቂያ” ወይም፣ “ሕዝባዊ ስብከት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።