am_tw/bible/other/precious.md

1.1 KiB

ውድ፣ የተወደደ፣ ክቡር

“ውድ” የሚለው ቃል በጣም የተወደዱ፣ በጥቂቱ የሚገኙ ወይም ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸውን ሰዎች ወይም ነገሮችን ያመለክታል።

  • “ክቡ ድንጋይ” ወይም፣ “የከበረ ዕንቁ” የተለያየ መልክ ያላቸውን ወይም ውብ የሚያደርጋቸው ባሕርያት ያላቸው ድንጋዮችና ማዕድኖችን ያመለክታል።
  • ዕንቁ፣ አልማዝና ኤመራልድ የከበሩ ድንጋዮች ዐይነት ናቸው።
  • ወርቅና ብርም፣ “የከበሩ ድንጋዮች” ይባላሉ።
  • ሕዝቡ በእርሱ ፊት የከበሩ (ብርቅ) መሆናቸውን ያህዌ ይናገራል (ኢሳይያስ 43፡4)
  • ገርና ጭምት መንፈስ በእግዚአብሔር ፊት ክብሩ ዋጋ እንዳለው ጴጥሮስ ጽፏል (1ጴጥሮስ 3፡4)።
  • ይህ ቃል፣ “ክቡር” ወይም፣ “በጣም ውድ” ወይም፣ “ብርቅ” ወይም፣ “ከፍ ያለ ዋጋ (ግምት) ያለው” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።