1.1 KiB
1.1 KiB
ውድ፣ የተወደደ፣ ክቡር
“ውድ” የሚለው ቃል በጣም የተወደዱ፣ በጥቂቱ የሚገኙ ወይም ከፍ ያለ ዋጋ ያላቸውን ሰዎች ወይም ነገሮችን ያመለክታል።
- “ክቡ ድንጋይ” ወይም፣ “የከበረ ዕንቁ” የተለያየ መልክ ያላቸውን ወይም ውብ የሚያደርጋቸው ባሕርያት ያላቸው ድንጋዮችና ማዕድኖችን ያመለክታል።
- ዕንቁ፣ አልማዝና ኤመራልድ የከበሩ ድንጋዮች ዐይነት ናቸው።
- ወርቅና ብርም፣ “የከበሩ ድንጋዮች” ይባላሉ።
- ሕዝቡ በእርሱ ፊት የከበሩ (ብርቅ) መሆናቸውን ያህዌ ይናገራል (ኢሳይያስ 43፡4)
- ገርና ጭምት መንፈስ በእግዚአብሔር ፊት ክብሩ ዋጋ እንዳለው ጴጥሮስ ጽፏል (1ጴጥሮስ 3፡4)።
- ይህ ቃል፣ “ክቡር” ወይም፣ “በጣም ውድ” ወይም፣ “ብርቅ” ወይም፣ “ከፍ ያለ ዋጋ (ግምት) ያለው” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።