ቃል መግባት
“ቃል መግባት” አንድ ነገር ለማድረግ ወይም ለመስጠት ተስፋ መስጠት ማለት ነው።
- ከብሉይ ኪዳን እንደምንመለከተው የእስራኤል ባለ ሥልጣኖች ለንጉሥ ዳዊት ታማኝ ለመሆን ቃል ገብተው ነበር።
- “ቃል መግባት” የሚለው ቃል ዕዳው እንደሚከፈል መያዣ እንዲሆን አንድን ነገር መስጠትን ወይም ተስፋ መስጠትንም ያመለክታል።
- የተገባው ቃል ሲፈጸም እንደ መያዣ ተሰጥቶ የነበረው ዕቃ ለባለቤቱ ይመለሳል።