am_tw/bible/other/persecute.md

904 B

ማሳደድ፣ ስደት

አንድን ሰው ማሳደድ ደጋግሞ ማጥቃት ወይም እርሱ ላይ የጭካኔ ተግባር መፈጸም ነው።

  • አንድን ሰው ብቻ፣ ትንንሽ ቡድኖችን ወይም ብዙ ቁጥር ያላቸው ሰዎችን ማሳደድ ይቻላል።
  • እርሱ የሚያስተምረውን ባለ መቀበላቸው የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎችና የሮም መንግሥት ክርስቲያኖችን አሳድደዋል። ይሁን እንጂ፣ አማኞች ስለ ኢየሱስ መስበካቸውንና ማስተማራቸውም አልተዉም፤ ቤተ ክርስቲያንም እያደገች ሄደች።
  • “ማሳደድን” ለመተርጎም ሌሎች ቃሎች፣ “መበደል” ወይም፣ “ማንገላታት” ወይም፣ መጨቆን” ወይም፣ “በጥላቻ መነሣት” የተሰኙት ናቸው።