am_tw/bible/other/perfect.md

1.1 KiB
Raw Permalink Blame History

ፍጹም

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ፍጹም” የሚለው ቃል በክርስትና ሕይወታችን አስተዋዮችን በሳሎች ሆኖ መገኘትን ነው። አንዳንዴ “ፍጹም” የሚለው ቃል የተሟላና እንከን የሌለበት እስኪሆን ድረስ በክርስትና ሕይወት ማደግ ማለትም ይሆናል።

  • አንድ ክርስቲያን ፍጹምና በሳል ሆነ ሲባል ታዛዥ፣ ኀጢአት የሌለው ሆነ ማለት ነው።
  • “ፍጹም” “የተሟላ” ወይም፣ “ሙሉ” መሆን ማለትም ይሆናል።
  • በመከራ መጽናት፣ አማኙ ውስጥ ሙሉነትንና ብስለትን እንደሚያስገኝ አዲስ ኪዳን ውስጥ ያለው የያዕቆብ መልእክት ይናገራል።
  • ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን ሲያጠኑና ለቃሉ ሲታዘዙ በባሕርያቸው ውስጥ ክርስቶስን እየመሰሉ ስለሚሄዱ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ሙሉና በሳሎች ይሆናሉ።