am_tw/bible/other/peaceoffering.md

967 B

የኅብረት መሥዋዕት

“የኅብረት መሥዋዕት” እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር እንዲያቀርቡ ከታዘዙት በርካታ የመሥዋዕት ስጦታዎች አንዱ ነበር። “የምስጋና መሥዋዕት” ወይም፣ “የሰላም መሥዋዕት” ተብሎም ይጠራል።

  • ይህ መሥዋዕት ምንም ጉድለት የሌለበት እንስሳ መሥዋዕት ማቅረብን፣ ደሙን መሠዊያው ላይ መርጨትንና በተለያየ ሁኔታ የተቀረውን የእንስሳውን አካልና ስቡን ማቃጠልንም ይጨምራል።
  • ከዚህ በተጨማሪ በሚቃጠለው መሥዋዕት ላይ የሚቃጠለውን እርሾ ያለበትና የሌለበት እንጀራም መሥዋዕት ይቀርባል።
  • ካህኑና መሥዋዕቱን የሚያቀርበው ሰው የቀረበውን መሥዋዕት እንዲበሉ ይፈቀድላቸዋል።