967 B
967 B
የኅብረት መሥዋዕት
“የኅብረት መሥዋዕት” እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር እንዲያቀርቡ ከታዘዙት በርካታ የመሥዋዕት ስጦታዎች አንዱ ነበር። “የምስጋና መሥዋዕት” ወይም፣ “የሰላም መሥዋዕት” ተብሎም ይጠራል።
- ይህ መሥዋዕት ምንም ጉድለት የሌለበት እንስሳ መሥዋዕት ማቅረብን፣ ደሙን መሠዊያው ላይ መርጨትንና በተለያየ ሁኔታ የተቀረውን የእንስሳውን አካልና ስቡን ማቃጠልንም ይጨምራል።
- ከዚህ በተጨማሪ በሚቃጠለው መሥዋዕት ላይ የሚቃጠለውን እርሾ ያለበትና የሌለበት እንጀራም መሥዋዕት ይቀርባል።
- ካህኑና መሥዋዕቱን የሚያቀርበው ሰው የቀረበውን መሥዋዕት እንዲበሉ ይፈቀድላቸዋል።