am_tw/bible/other/patient.md

831 B

ታጋሽ፣ ትዕግሥት

“ታጋሽ” እና፣ “ትዕግሥት” የሚለው ቃል አስቸጋሪ የሆነ ሁኔታ መቋቋምን ወይም በዚያ ውስጥ በጽናት መኖርን ያመለክታል። አብዛኛውን ጊዜ ትዕግሥት መጠበቅንም ይጨምራል።

  • አንድን ሰው መታገሥ ያ ሰው የቱንም ያህል በደል ቢፈጽም እርሱን መውደድና ይቅር ማለት ማለት ነው።
  • ችግር ሲገጥማቸው የእግዚአብሔር ሕዝብ መታገሥና እርስ በርሳቸውም ትዕግሥተኞች መሆን እንደሚገባቸው መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል።
  • ከምሕረቱ የተነሣ ቅጣት የሚገባቸው ኀጢአተኞች ቢሆኑም እግዚአብሔር ሕዝቡን ይታገሣል።