am_tw/bible/other/pagan.md

941 B

አረማዊ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “አረማዊ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ያህዌን ሳይሆን ሐሰተኛ አምላኮችን የሚያመልኩ ሰዎች ለማመልከት ነበር።

  • ከእነዚያ ሰዎች ጋር የተያያዘ ማንኛውም ነገር ማለትም የሚያመልኩበት መሠዊያ፣ የሚፈጽሙት ሃይማኖታዊ ሥርዓትና እምነታቸው ጭምር፣ “አረማዊ” ይባላል።
  • የአረማውያን እምነት ተፈጥሮን ወይም ከአንዱ እውነተኛ አምላክ ከያህዌ ውጪ ብዙ አምላኮች ማምለክንም ይጨምራል።
  • አንዳንድ የአረማውያን ሃይማኖቶች የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚደረግበት አምልኮን ወይም እንደ አንድ የአምልኳቸው ክፍል ሰዎችን መሥዋዕት ማቅረብንም ያካትታል።