am_tw/bible/other/oath.md

1.3 KiB

መሐላ

በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት አንዳች ነገር ለማድረግ የሚሰጥ ውል ያለው ተስፋ ቃል ነው። መሐላ የሚያደርግ ሰው የሰጠውን ተስፋ የመፈጸም ግዴታ አለበት።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መሐላ” ቃል መግባት ማለት ነው።
  • “በ . . . መማል” ከተባለ መሐላው የሚደረግበት መሠረት ወይም ሥልጣን እንዲሆን የአንድን ሰው ስም በመጥራት በይፋ መናገር ማለት ነው።
  • አንዳንዴ ቃሉ፣ “መሐላ መማል” በሚል መልኩ ይቀርባል።
  • የጉድጓድ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ ኪዳን ለማድረግ አብርሃምና አቢሜሌክ ተማምለው ነበር።
  • ከአብርሃም ዘሮች መካከል ለልጁ ለይስሐቅ ሚስት እንዲፈልግለት አብርሃም አገልጋዩን ቃል አስገብቶት ወይም አስምሎት ነበር።
  • ለሕዝቡ የገባውን ተስፋ ለመፈጸም እግዚአብሔር ራሱ ምሎ ነበር።
  • በዚህ ዘመን፣ “መሐላ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የሚውልበት ሁኔታ እንዲሁ ከንቱ ቃል መናገር ሲሆን፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም ጋር አይስማማም።