am_tw/bible/other/mystery.md

745 B

ምሥጢር፣ የተደበቀ እውነት

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፣ “ምሥጢር” የማይታወቅ ወይም ለመረዳት የሚያዳግት አሁን ግን እግዚአብሔር የገለጠውን ነገር ያመለክታል።

  • የክርስቶስ ወንጌል ባለፉት ዘመኖች ያልታወቀ ምሥጢር እንደ ነበር አዲስ ኪዳን ያመለክታል።
  • ምሥጢር ተብሎ ከተገለጠ ነገር አንዱ የአይሁድና የአሕዛብ በክርስቶስ አንድ መሆን ነበር።
  • ይህ ቃል፣ “የተሰወረ” ወይም፣ “የተደበቀ ነገር” ወይም፣ “ያልታወቀ ነገር” ተብሎ መተርጎም ይችላል።