am_tw/bible/other/mourn.md

1.6 KiB

ማልቀስ፣ ለቅሶ

“ማልቀስ” እና፣ “ለቅሶ” የተሰኙት ቃሎች ጥልቅ የሐዘን መገለጫዎች ሲሆኑ፣ ብዙውን ጊዜ የሚያያዙት ሰው ሲሞት ከሚደረግ ሐዘን ጋር ነው። ብዙ ባሕሎች ሐዘንና ትካዜያቸውን የሚገልጡበት ውጫዊ እንቅስቃሴን ይጨምራል።

  • እስራኤላውያንና በጥንት ዘመን የነበሩ ሌሎች ሕዝቦች ለቅሶዋቸውን የሚገልጡት ጮኽ ብሎ በሚሰማ ዋይታ ወይም እንጉርጉሮ ሲሆን፣ በአብዛኛው አሁን ያሉ ሕዝቦች ከሚያደርጉት ጋር ይመሳሰላል።
  • ብዙውን ጊዜ ሰውየው ከሞተበት ጊዜ አንሥቶ መቃብር ውስጥ ከገባ ጥቂት ጊዜ በኋላ ድምፃቸውን አሰምተው ዋይ እንዲሉ አልቃሾች ይቀጠሩ ነበር። አብዛኛውን ጊዜ እነዚህ አልቃሾች ሴቶች ነበሩ።
  • መደበኛው የለቅሶ ጊዜ ሰባት ቀን ሲሆን፣ እስከ ሰለሣ ቀን (ሙሴና አሮን ሲሞቱ እንደ ተደረገው) ወይም እስከ ሰባ ቀን ድረስ (ያዕቆብ ሲሞት እንደ ተደረገው) ይቆይ ነበር።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በኀጢአት ምክንያት ስለ “ማልቀስ” ሲናገር ይህን ቃል በምሳሌነት ይጠቀማል። ኀጢአታችን ምን ያህል እግዚአብሔርን፣ ራሳችንንና ሌሎች ሰዎችን ምን ያህል እንደ ጎዳ በማሰብ ጥልቅ የሐዘን ስሜትንም ይጨምራል።