am_tw/bible/other/kingdom.md

1.3 KiB

መንግሥት

መንግሥት በንጉሥ የሚገዛ የሰዎች ቡድን ነው። ንጉሥ ወይም ሌሎች ገዦች የሚቆጣጠሩትና በሥልጣን የሚያስተዳድሩትንም አካባቢ ወይም ፖለታካዊ አገርንም ያመለክታል።

  • መንግሥት ማንኛውም ዐይነት መልክዓ ምድራዊ መጠን ሊኖረው ይችላል። ንጉሥ ሕዝብን፣ አገርን ወይም አንድ ከተማ ብቻ ሊገዛ ይችላል።
  • “መንግሥት” የሚለው ቃል፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት” በተሰኘው ሐረግ መሠረት መንፈሳዊ ግዛትን ወይም ሥልጣንን ማመልከትም ይችላል።
  • እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ ገዢ ቢሆንም፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት” የሚለው ሐረግ በተለይ የሚያመለክተው በኢየሱስ ያመኑትና ለእርሱ ሥልጣን በተገዙት ላይ እርሱ ያለውን ገዢነት ወይም ሥልጣን ነው።
  • ሰይጣን በምድር ያሉ ብዙ ነገሮችን ለጊዜው የሚገዛበት፣ “መንግሥት” እንዳለው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። የእርሱ መንግሥት ክፉ ነው፣ “ጨለማ” ተብሎ ይጠራል።