808 B
808 B
ዳኛ፣ ፈራጅ
አስተዳደራዊ፣ ሕጋዊ ወይም መንፈሳዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ትክክልና ስሕተት የሆኑ ነገሮችን የሚወስን ሰው ዳኛ ወይም ፈራጅ ይባላል።
- ትክክል ወይም ስሕተት የሆኑ ነገሮችን በተመለከተ ፍጹም ዳኛ ወይ ፈራጅ እርሱ በመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ዳኛ የሚባለው እግዚአብሔር ነው።
- የእስራኤል ሕዝብ ወደ ተስፋው ምድር ከገቡ በኋላና በንጉሦች ከመተዳደራቸው በፊት በችግር ጊዜ የሚመሯቸው ዳኞች እግዚአብሔር ሾሞላቸው ነበር። ብዙ ጊዜ እነዚህ ዳኞች ከጠላቶቻቸው አድነዋቸዋል።