am_tw/bible/other/judgeposition.md

808 B

ዳኛ፣ ፈራጅ

አስተዳደራዊ፣ ሕጋዊ ወይም መንፈሳዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ትክክልና ስሕተት የሆኑ ነገሮችን የሚወስን ሰው ዳኛ ወይም ፈራጅ ይባላል።

  • ትክክል ወይም ስሕተት የሆኑ ነገሮችን በተመለከተ ፍጹም ዳኛ ወይ ፈራጅ እርሱ በመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ዳኛ የሚባለው እግዚአብሔር ነው።
  • የእስራኤል ሕዝብ ወደ ተስፋው ምድር ከገቡ በኋላና በንጉሦች ከመተዳደራቸው በፊት በችግር ጊዜ የሚመሯቸው ዳኞች እግዚአብሔር ሾሞላቸው ነበር። ብዙ ጊዜ እነዚህ ዳኞች ከጠላቶቻቸው አድነዋቸዋል።