am_tw/bible/other/incense.md

1.4 KiB

ዕጣን

ዕጣን እሳት ላይ በሚደረግበት ጊዜ ደስ የሚል ሽታ የሚሰጥ ጣፋጭ መዓዛ ያላቸው ቅመሞድ ድብልቅ ነው። እነዚህ ቅመሞች ከዕፅዋት ክፍሎች የተገኙ ሲሆኑ፣ በጣም ጥቃቅን እስኪሆኑ ድረስ ይደቅቃሉ።

  • ለእርሱ መሥዋዕት የሚሆን ዕጣን እንዲያጨሱ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሮአል። ዕጣኑ የሚቀመመው እግዚአብሔር ባዘዘው መሠረት ሁሉም እኩል መጠን ካላቸው አምስት ቅመሞች ነበር። የተቀደሰ ዕጣን በመሆኑ፣ ለሌላ ዓይነት ዓላማ እንዲውል አይፈቀድም ነበር።
  • ለዕጣን ማጨሻ ብቻ የተመደበ የወርቅ መሠዊያ ነበር።
  • በእያንዳንዱ የጸሎት ጊዜ ቢያንስ በቀን አራት ጊዜ ዕጣኑ መጨስ ነበረበት።
  • በተጨማሪም የሚቃጠል ሥጋ መሥዋዕት በሚቀርብበት ጊዜ ሁሉ ዕጣን መጨስ ነበረበት።
  • የዕጣን መጨስ ጸሎትንና ከሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር የሚወጣ አምልኮን ይወክላል።
  • ዕጣን የሚለውን ቃል ለመተርጎም ሌሎች መንገዶች፣ “ጣፋጭ ሽታ ያለው ቅመም” ወይም፣ “ጥሩ ሽታ ያላቸው ተክሎች” የተሰኙ ናቸው።