am_tw/bible/other/hard.md

1.1 KiB

ጠንካራ፣ ጥንካሬ

“ጠንካራ” የሚለው ቃል እንደ ዐውዱ ሁኔታ የተለያዩ ትርጕሞች ይኖሩታል። ብዙዎን ጊዜ የሚያመለክተው አስቸጋሪ፣ አዳጋች ወይም የማይበገር ነገርን ነው።

  • “ልበ ጠንካራ” የተሰኘው ፈሊጣዊ አነጋገር ግትርና ንስሐ የማይገቡ ሰዎችን ያመለክታል። ይህ አነጋገር ከክፉ ሥራቸው የተነሣ ከባድ መከራ ቢደርስባቸው እንኳ በእግዚአብሔር ላይ ማመፃቸውን የሚቀጥሉ ሰዎች መገለጫ ነው።
  • “የልብ ጥንካሬ” እና “የልባቸው ጥንካሬ” የሚለው ምሳሌያዊ ገለጻም እንዲሁ ግትር አለመታዘዝን ያመለክታል።
  • “ጠንክሮ መሥራት” ወይም፣ “ጠንክሮ መሞከር” ማለት በጽናትና በትጋት አንድን ነገር ማድረግ፣ አንድን ነገር ጥሩ አድርጎ ለመሥራት ከባድ ጥረት ማድረግን ያመለክታል።