am_tw/bible/other/hand.md

13 lines
1.8 KiB
Markdown

# እጅ፣ ቀኝ እጅ
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “እጅ” የሚለው ቃል በምሳሌያዊ አነጋገር በበርካታ ቦታዎች ጥቅም ላይ ውሏል።
* ብዙውን ጊዜ “እጅ” የእግዚአብሔርን ኀይልና ሥራ ለማመልከት ተጠቅሷል፤ “እጁ ይህን ሁሉ አላደረገችምን?” እንደሚለው።
* “በእጅ ተላልፎ መሰጠት” የሚለው አገላለጽ አንድ ሰው በሌላው ሰው ቁጥጥር ሥልጣን ሥር እንዲሆን አሳልፎ መስጠትን ያመለክታል።
* “እጆችን መጫን” አንድን ሰው ለእግዚአብሔር አገልግሎት ለመለየት ወይም እንዲፈወስ ለመጸለይ እጆችን እርሱ ላይ ማድረግን ያመለክታል።
* “እጅ” የሚለው ቃል በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ሲውል፣ “እጆችህን አትጫን” ማለትም ማንንም አትጉዳ የሚለውን ይጨምራል።
* “ከ . . . እጅ ማዳን” አንድ ሰው ሌላውን እንዳይጎዳ ማስቆም ማለት ነው።
* “በቀኝ እጅ” በቀኝ በኩል ወይም በቀኝ ወገን ቦታ መያዝ ማለት ነው።
* በ . . . እጅ” የሚለው ሐረግ በዚያ ሰው እጆች የተከናወነ ወይም የተደረገ ተግባር ያመለክታል፤ ለምሳሌ፣ “በጌታ እጅ” ማለት ያንን ያደረገ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።
* ጳውሎስ፣ “ይህን በእጄ የጻፍኩ እኔ ነኝ” ሲል ያ መልእክት የተጻፈው እርሱ በቃል በሚነግረው በሌላው ሰው እጅ ሳይሆን በእርሱ ራሱ እጅ የተጻፈ መሆኑን ያመለክታል።