am_tw/bible/other/goat.md

1.9 KiB

ፍየል

ፍየል መጠነኛ ቁመት ያለው፣ ከበግ ጋር የሚመሳሰልና በዋነኛነት ደረጃ ወተትና ሥጋ ለማግኘት ሰዎች የሚያረቡት ባለ አራት እግር እንስሳ ነው። የፍየል ግልገል “ወጠጤ” ይባላል።

  • እንደ ብጎች ሁሉ ፍየሎችም መሥዋዕት ይቀርቡ ነበር፤ በተለይም ለመሥዋዕት የሚፍለጉት በፋሲካ በዓል ነበር።
  • ምንም እንኳ ፍየሎች ከበጎች ጋር ቢመሳሰሉም በግልጽ የሚታዩ ጥቂት ልዩነቶችም አሏቸው።
  • ፍየሎች ጥቁርና ሻካራ ጠጉር አላቸው፤ የበጎች ጠጉር ግን ሱፍ ልብስ ይሠራበታል።
  • የፍየል ጭራ ወደ ላይ የቆመ ሲሆን የበግ ጭራ ግን የተንጠለጠለ ነው።
  • ፍየሎች ጉጉ ስለሆኑ፣ ሌሎች ፍየሎች ባሉበት ቦታ አይሆኑም ወይም ሌሎች በሚሄዱበት አይሄዱም፤ በጎች ግን ከሌሎች በጎች ጋር አብረው መሆን ምቾት ይሰጣቸዋል፤ እረኛውን የመከተል ባሕርይም አላቸው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ፍየሎች በእስራኤል በዋናነት ደረጃ ወተት የሚገኘው ከፍየሎች ነበር።
  • የፍየሎች ቆዳ ድንኳን የወይን ጠጅ የሚያዝበት ስልቻ መመሥሪያ ያገለግል ነበር።
  • በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን ፍየሎች የኀጢአተኞች ምሳሌ ተደርገው ይቀርቡ ነበር፤ ምናልባትም ለዚህ ምክንያቱ ፍየሎች ከሚጠቃቸው ሰው የመኮብለል ብርቱ ዝንባሌ ስላላቸው ሊሆን ይችላል።
  • እስራኤላውያን ፍየሎችን እንደ የኀጢአት ተሸካሚ ምሳሌ ያደርጓቸው ነበር።