am_tw/bible/other/gnashteeth.md

1.0 KiB

ጥርስ ማፋጨት

ጥርስ ማፋጨት ማለት ጥርሶችን በማያያዝ ወደ ፊት ወደ ኋላ በማድረግ ወይም ግራና ቀኝ በማድረግ እርስ በርሳቸው እንዲፋጩ ማድረግ ማለት ነው። ይህ ብዙውን ጊዜ የሚያሳየው ከባድ ስቃይን (ሕመምን) ወይም ቊጣን ነው።

  • ገሃነም ውስጥ የሚኖሩ ከሚደርስባቸው ከባድ ስቃይ የተነሣ ጥርሳቸውን እንደሚያፏጩ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
  • የአገርህ ባሕል አንድ ሰው ሲቆጣ ጥርሱን የማያፋጭ ከሆነ ይህ ሐረግ፣ “በቍጣ ጥርስን ማፋጨት” ብሎ መተርጎም ይቻላል። ወይም በአንተ ባሕል ሰዎች ሲቆጡ የሚያደርጉትን እንደ እግርን አንስቶ መሬቱን በኀይል መርገጥን የላይ የታች ጥርሶችን ግጥም አድርጎ መያዝን ወይም መጮኽን የመሳሰሉ ቃሎች መጠቀም ይቻላል።