1.2 KiB
1.2 KiB
ማክበር
አንድ ሰው ወይም ነገር ምን ያህል ታላቅና አስፈላጊ መሆኑን ማሳየት ወይም መናገር ማለት ነው። ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ክብር መስጠት” ማለት ነው።
- እርሱ ስላደረገው ድንቅ በመናገር ሰዎች እግዚአብሔርን ማክበር ይችላሉ።
- ለእርሱ ክብር በሚያስገኝ መንገድ በመኖርና እርሱ ምን ያህል ታላቅና ቸር መሆኑን በማሳየት እግዚአብሔርን ማክበርም ይችላሉ።
- መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱን አከበረ ሲል ብዙውን ጊዜ በተአምራቱ አማካይነት አስደናቂ ታላቁነቱን አሳየ ማለቱ ነው።
- የወልድን ፍጹምነት፣ ውበትና ታላቅነት ለሰዎች በመግለጥ እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድን ያከብራል።
- በክርስቶስ የሚያምን ሁሉ ከእርሱ ጋር ይከብራል። ከሞት በሚነሡበት ጊዜ ክብሩን እንዲያንጸባርቁና ለፍጥረት ሁሉ ጸጋውን ለማሳየት ይለወጣሉ።