am_tw/bible/other/glorify.md

10 lines
1.2 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-04 19:07:37 +00:00
# ማክበር
አንድ ሰው ወይም ነገር ምን ያህል ታላቅና አስፈላጊ መሆኑን ማሳየት ወይም መናገር ማለት ነው። ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ክብር መስጠት” ማለት ነው።
* እርሱ ስላደረገው ድንቅ በመናገር ሰዎች እግዚአብሔርን ማክበር ይችላሉ።
* ለእርሱ ክብር በሚያስገኝ መንገድ በመኖርና እርሱ ምን ያህል ታላቅና ቸር መሆኑን በማሳየት እግዚአብሔርን ማክበርም ይችላሉ።
* መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱን አከበረ ሲል ብዙውን ጊዜ በተአምራቱ አማካይነት አስደናቂ ታላቁነቱን አሳየ ማለቱ ነው።
* የወልድን ፍጹምነት፣ ውበትና ታላቅነት ለሰዎች በመግለጥ እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድን ያከብራል።
* በክርስቶስ የሚያምን ሁሉ ከእርሱ ጋር ይከብራል። ከሞት በሚነሡበት ጊዜ ክብሩን እንዲያንጸባርቁና ለፍጥረት ሁሉ ጸጋውን ለማሳየት ይለወጣሉ።