am_tw/bible/other/father.md

1.1 KiB

አባት፣ ጥንተ አባት

ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “አባት” የአንድ ሰው ወንዱ ወላጅ ማለት ነው። ይህን ቃል በተመለከተ በርካታ ምሳሌያዊ አነጋገሮች አሉት።

  • ብዙውን ጊዜ፣ “አባት” ወይም “ጥንተ አባት” የተሰኙ ቃሎች ጥቅም ላይ የሚውሉት በቀድሞ ዘመን የነበሩ ጥንታውያን ወላጆችን ለማማልከት ነው።
  • “የ…አባት” የሚለው አገላለጽ የአንድ አገር መሪ ወይም መሥራችን የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው። ለምሳሌ ዘፍጥረት 4 ላይ፣ “እርሱም በድንኳን ውስጥ ለሚቀመጡ ሁሉ አባት ነበር” ሲል፣ “ድንኳን ውስጥ ለመኖር የመጀመሪያ ለሆኑት ሕዝቦች ጎሳ መሪ” ማለት ሊሆን ይችላል።
  • ሐዋርያው ጳውሎስ ወንጌልን በማካፈል ክርስቲያን እንዲሆኑ የረዳቸው ሰዎች “አባት” በማለት በምሳሌያዊ መልኩ ራሱን ይጠራል።