9 lines
874 B
Markdown
9 lines
874 B
Markdown
# ጾም
|
|
|
|
መጾም ምግብን ወይም አንዳንድ የምግብ ዐይነቶችንና መጠጦችን ለተወሰነ ጊዜ ማቆም ነው።
|
|
|
|
* ጾም ሰዎች ትኩረታቸውን እግዚአብሔር ላይ እንዲያደርጉና በምግብ አስተሳሰባቸው ሳይበታተን መጸለይ እንዲችሉ ይረዳል።
|
|
* የተሳሳተ ዓላማ ይዞ በመጾም ኢየሱስ የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎችን ተቃውሞ ነበር። ይጾሙ የነበረው ምን ያህል ሃይማኖተኞች መሆናቸውን ሌሎች እንዲያዩላቸው ነበር።
|
|
* አንዳንዴ ሰዎች የሚጾሙት በአንድ ነገር ምክንያት በጣም ማዘናቸውንና መተከዛቸውን ለማሳየት ነው።
|
|
* ይህ ቃል፣ “መመገብን መተው” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
|