am_tw/bible/other/famine.md

1014 B

ችጋር

ችጋር በመላው አገር ወይም አካባቢ የምግብ እጥረትን የሚጨምር ጥፋት ሲስፋፋ ማለት ነው።

  • የዝናብ አለመኖርን፣ ጥሩ ያልሆነ የአየር ሁኔታን፣ የሰብል መቀጨጭ ወይም ተባዮችን በመሳሰሉ ተፈጥሮአዊ ምክንያቶች የተነሳ የምግብ እጥረት ይከሰታል።
  • ከጦርነት ወይም መልካም ካልሆነ አስተደድር የተነሣም የምግብ እጥረት ሊኖር ይችላል።
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው በእርሱ ላይ ኀጢአት ያደረገ ሕዝብን ለመቅጣት እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ ራብ እንዲኖር ያደርግ ነበር።
  • አሞጽ 8፣11 ላይ “ራብ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው ለእነርሱ ባለመናገር ሕዝቡን ይሚቀጣበት ጊዜ እንደሚመጣ በሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር ነው።