am_tw/bible/other/exile.md

870 B

ምርኮ፣ ምርኮኛ

“ምርኮ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከአገራቸው ርቀው ሌላ ቦታ እንዲኖሩ የተገደዱ ሰዎችን ያመለክታል።

  • ብዙ ጊዜ ሰዎች ለቅጣት ወይም በፖለቲካ ምክንያት ከአገር ውጪ እንዲኖሩ ይገደዳሉ።
  • በጦርነት የተሸነፉ ሰዎች ለእርሱ እንዲሠሩ ተብሎ አሸናፊው ሰራዊት አገር ውስጥ እንዲኖሩ ይወሰዳሉ።
  • የባቢሎን ምርኮ የሚባለው ብዙ የአይሁድ ዜጎች ከአገራቸው ተወስደው በባቢሎን እንዲኖሩ የተገደዱበት የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ነው።
  • “ምርኮኛ” የሚለው ቃል ከአገር ከወገናቸው ርቀው በባዕድ ምድር የሚኖሩ ሰዎችን ያመለክታል።